የባለትዳሮች ህብረት አገልግሎት በኢትዮጵያዉያን ክርስቲያኖች ኅብረት ቤተክርስትያን አስተዳደር መመሪያና መተዳደሪያ ደንብ መሰረት፤ የአጥብያ ቤተክርስቲያን አካል ሆኖ የሚሰራ ነዉ ። ዋና የአገልግሎቱ ትኩረት ባልና ሚስት እርስ በእርስ ሊኖራቸዉ የሚገባዉን ግንኙነት በእግዚአብሔር ቃል መሰረት በፍቅር፤ በመከባበርና አንዱ ሌላዉን ለመርዳት (to understand each other) በመጣርና በመተሳሰብ ፤ በመደጋገፍ ላይ እንዲመሰረትና እንዲያድግ ማበረታታት ነዉ ።
አገልግሎቱ አጥቢያ ቤተክርስተያንዋ የተሰጣትን ዋና የማስተማር ተልእኮዋን ቤተሰብን በተመለከተ መስክ (topics/subject) ረገድ ለመተካት ሳይሆን፤ ስራዋን በማገዝና በመ ደገፍ እንደ አንድ የአካልዋ ክፍል ለተልኮዋ ስኬት መተባበር ነዉ ።
አገልግሎቱ በተለይ የታወቀበትና በየዓመቱ በጉጉት በብዙዎች ዘንድ የሚጠበቀዉ ‘በፌበሪዎሪ’ አጋማሽ ላይ
የሚ ኪያሄደዉ “የፍቅረኞች ጊዜ” ነዉ ። በዚህ ጊዜ ባለትዳሮች በሚኖራቸው የሕብረት ጊዜ ትዳርን በተመለከተ የተለያዩ ትምህርቶች ይሰጣቸዋል።
እንደዚሁም በየጊዜው ባለትዳሮችን በተመለከተ፥ ትምህርታዊ አውደ ጥናቶችን (workshops) በማዘጋጀት፤ በቤተሰብ ነክ ጉዳዮች ላይ እግዚአብሔርን በማገልገል የተሰማሩትን ወንድሞችና እህቶችን ከዉጪም ሆነ ከዉስጥ በመጋበዝ የማነቃቂያና የማበረታቻ ፕሮግራሞችን ያስተባብራል ።